ከአባ ዕዝራ ዘደቂቀ እስጢፋኖስ
ሀራ ዘተዋህዶ የተሰኘው አፍቃሬ ማህበረ ቅዱሳን ድረገጽ በApril 19, 2013 ባወጣው ጽሁፍ እንደተለመደው በርካታ በሀሰት የተሞላ የፈጠራ ወሬ አስነብቧል፡፡ ከዚያም ባለፈ ቤተክርስቲያንን በዘረኛ ፖለቲካው ለመከፋፈል በዘረኝነት የተለወሰ መርዙን ረጭቷል፡፡ “የትግራይ ተወላጆች የግቢውን አመራር ሙሉ በሙሉ እንረከበዋለን፡፡ ከዚህ በኋላ ቤተ ክርስቲያን በትግራዎች እንጂ በአማራ አትመራም፡፡” ብለዋል በማለት ዘረኛ አመለካከቱን እግዚአብሔርን ሳይፈራ ሰውንም ሳያፍር በገሃድ ተናግሯል፡፡
የማቅ ሰዎች ፈሊጥ የጐደላቸው በመሆናቸው በሃይማኖት ሽፋን የሚያራምዱትን ፖለቲካ በቅጡ የተረዱት
↧